BBC News, አማርኛ - ዜና
ዜና
በቅርቡ "በመፈንቅለ መንግሥት ሥልጣን የተቆጣጠረውን ቡድን አስወግደን" መቀለ እንገባለን የሚሉት ቡድኖች እነማን ናቸው?
በፕሪቶሪያው ስምምነት የተመሠረተውን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የሚተካ እና የቀድሞውን ምክር ቤት እና ፕሬዝዳንት ወደ ሥልጣን መመለሱን የሚገልጽ ዜና ከተሰማ ሳምንታት ተቆጥረዋል። ይህንን የሚቃወሙ የትግራይ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ማኅበራት የራሳቸውን ስብስብ በመፍጠር "የሰላም እና የለውጥ ምክር ቤት" አቋቁመዋል። ዓላማቸው ምንድን ነው?
ቀጥታ, ኢራን በጦርነቱ ለደረሰባት ውድመት ካሳ እንዲሁም የአሜሪካ ወታደሮች እንዲወጡ የሚጠይቅ ሃሳብ አቀረበች
አዲሱ የሰላም ዕቅድ በሊባኖስ ውስጥ የሚካሄደውን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች የሚደረጉ ጦርነቶች እንዲቆሙ፣ በኢራን አቅራቢያ የሰፈሩ የአሜሪካ ወታደሮች እንዲወጡ እና በጦርነቱ ለደረሰባት ውድመት ካሳን እንዲከፈላት የሚጠይቅ መሆኑን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ግብፅ እና ኤርትራ የቀይ ባሕር ጉዳይ የሚመለከተው "የጠረፉን አገራት ብቻ ነው" አሉ
ቀይ ባሕር ላይ የሚደረግ የትራንስፖርት እንቅስቃሴን እና የወደብ ትስስርን የተመለከተ ስምምነት የተፈራረሙት ግብፅ እና ኤርትራ፤ የቀይ ባሕር ጉዳይ የሚመለከተው "የቀይ ባሕር ጠረፍ አገራትን ብቻ" እንደሆነ ገለጹ። ቀይ ባሕርን ከሚያዋስኑ የባሕር ዳርቻ አገራት "ብሔራዊ ደኅንነት ጋር ቀጥተኛ ትስስር" እንዳለው በመጥቀስም "የቀይ ባሕር አጎራባች ያልሆነ አካል ቀይ ባሕርን በሚመለከቱ ጉዳዮች መግባት የለበትም" ማለታቸውም ተዘግቧል።
የቢቢሲ አማርኛ ዩቲዩብ ቻናልን ይቀላቀሉ
የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ - 2018
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አገራዊ ምክክር እየተደረገ ያለው የአገሪቱን መሪ የሥልጣን ዘመን "ለመገደብ" መሆኑን ተናገሩ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አገራዊ ምክክር እየተደረገ ያለው በአገሪቱ ሕገ መንግሥት ያለ ማብቂያ የተጠቀመጠውን የአገሪቱን መሪ የሥልጣን ዘመን "ለመገደብ" መሆኑን ተናገሩ። መንግሥት "ሥልጣኑ በሕግ ተገድቦ" ሕገ መንግሥት እንዲሻሻል እየጠየቀ ባለበት ሁኔታ በአገራዊ ምክክሩ "አንወያይም" ያሉ አካላትን ተችተዋል።
ብልጽግና ፓርቲ፤ የአብን እና የኢዜማ አመራሮች በሚወዳደሩባቸው የምርጫ ክልሎች ዕጩ አላቀረበም
ገዢው ብልጽግና ፓርቲ ዕጩ ባላቀረበባቸው ከ80 በላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎች ውስጥ የተቃዋሚዎቹ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) አመራሮች የሚወዳደሩባቸው የምርጫ ክልሎች እንደሚገኙ ቢቢሲ ተገንዝቧል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መራጮች እንዲመዘገቡ የተለያዩ ጫናዎች እየተደረጉ መሆናቸውን ገለጸ
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በመራጮች የምዝገባ ሂደት ወቅት "ቤት ለቤት በመሄድ" ካርድ ውሰዱ ከሚል አንስቶ "ማኅበራዊ አገልግሎት ማግኘት" እንዲሁም "ከደሞዝ መቁረጥ ጋር በማያያዝ" በዜጎች ላይ ተጽዕኖ እስከማድረስ ያሉተግባራትን ማስተዋሉን ገለጸ።
ብልጽግና ፓርቲ ዕጩ ባላቀረበበት ትግራይ ክልል ምርጫ ይካሄዳል?
ብልጽግና ፓርቲ፤ ምርጫ የመካሄዱ ነገር አጠራጣሪ በሆነበት ትግራይ ክልል ለሚገኙ የፓርላማ እና የክልል ምክር ቤት መቀመጫዎች አንድም ዕጩ አለማቅረቡን ቢቢቢ የተመለከተው የዕጩዎች ዝርዝር ያሳያል። ስድስት ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች እና ሁለት ቅንጅቶች በበኩላቸው 101 ዕጩዎችን አስመዝግበዋል።
ባለፈው ምርጫ ብልጽግናን ከወከሉ የአዲስ አበባ ተመራጮች ውስጥ ከ60 በመቶ በላዩ በአዲስ ተተኩ
ብልጽግና ፓርቲ ግንቦት ላይ ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው ሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ ለአዲስ አበባ ከተማ ካቀረባቸው 154 ዕጩዎች ውስጥ 96 ያህሉ በባለፈው ምርጫ በመዲናዋ ያልተወዳደሩ እንደሆኑ ቢቢሲ ያደረገው ዳሰሳ ያሳያል። በመጪው ምርጫ በአዲስ አበባ ዕጩ ሆነው ካልቀረቡት ተመራጮች መካከል ምክትል ከንቲባው ጃንጥራር አባይ ይገኙበታል።
ከፍተኛ ውዝግብ ስላስነሳው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ ማን ምን አለ?
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአማራ እና ትግራይ ክልሎች መካካል "አከራካሪ ሆነው የቆዩ" የተባሉትን አምስት የምርጫ ክልሎች በተመለከተ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ደርሶኛል ያለውን ውሳኔ ይፋ ካደረገ በኋላ የሁለቱ ክልሎች የፖለቲካ ተዋንያን በየፊናቸው መግለጫዎችን አውጥተዋል። በትግራይ በኩል ጊዜያዊ አስተዳደሩን ጨምሮ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ፤ በአማራ በኩል የሚገኙት ደግሞ ለውሳኔው ድጋፋቸውን ገልጸዋል።
በምርጫ ለመሳተፍ በቅድመ ሁኔታ እና ሕጋዊነትን በማጣት መካከል የተወጠሩት የፖለቲካ ፓርቲዎች
አስር ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ስብስብ በዚህ ዓመት የሚካሄደው ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተዓማኒ እንዲሆን እና "ከአጃቢነት ያለፈ ተሳትፎ" እንዲኖራቸው የሚጠይቅ ቅድመ ሁኔታዎችን አቀረቡ። ራሳቸውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች አንድነት መድረክ (መድረክ) ሲሉ የሚጠሩት 10 የተቃዋሚ ፓርቲዎች ስብስብ ኅዳር 3/2018 ዓ.ም. በጋራ ባወጡት መግለጫ ላይ "ሕጋዊነትን ለመላበስ የሚደረጉ የፖለቲካ ትወናዎች" ሲሉ ከዚህ ቀደም የተደረጉ ምርጫዎችን በመኮነን፤ ምርጫዎቹ "ነፃ፣ ፍትሃዊ እና አሳታፊ፤ በውጤታቸውም ተዓማኒ እና በሕዝብ ተቀባይነት አላገኙም" ሲሉ ተችተዋል።
የቢቢሲ አማርኛ ዩቲዩብ ቪድዮዎች
ቪዲዮ, የደብረ ጽዮን በፕሬዝዳንትነት መሰየም ትግራይን ወዴት ይወስዳታል?
በትግራይ ሁለት ፕሬዝዳንቶች ተሹመዋል። ህወሓት የፕሪቶሪያ የግጭት ማቆም ስምምነት መፍረሱን በመጥቀስ ከጦርነት በፊት የነበረውን አስተዳደር መመለሱን አስታውቋል። ሌ/ጄኔራል ታደሰ በሥልጣን ላይ እያሉ ነው ደብረጽዮን ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት። ክልሉ እንዴት እዚህ ሁኔታ ላይ ደረሰ? የሌ/ጄነራል ታደሰ ዕጣ ፈንታስ ምን ሊሆን ይችላል?
ቪዲዮ, ለሦስተኛ ጊዜ የመግደል ሙከራ የተደረገባቸው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት
ቅዳሜ ምሽት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በርካታ የአሜሪካ ባለሥልጣናት በተገኙበት የእራት ግብዣ ላይ ጥቃት ለማድረስ የሞከረ ግለሰብ በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ስር ውሏል። ትራምፕን ለመግደል የሚደረግ ሙከራ አዲስ አይደለም። እስካሁን በፕሬዝዳንቱ ላይ የተቃጡት የመግደል ሙከራዎች ምን ይመስላሉ?
ቪዲዮ, የአሜሪካ እና የኢራን ተኩስ አቁም ስምምነት
ኢራን እና አሜሪካ የሆርሙዝ ወሽመጥ ተከፍቶ መርከቦች እንዲያልፉ የሚያስችል የሁለት ሳምንት የተኩስ አቁም ለማድረግ ተስማምተዋል። አገራቱን ሲያሸማግሉ የነበሩት የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሻሪፍ የተኩስ አቁሙ ወዲያውኑ ገቢራዊ እንደሆነ አስታውቀዋል። ሁለቱ አገራት እዚህ ስምምነት ላይ የደረሱት፤ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን ወሳኙን የባሕር መተላለፊያ ማክሰኞ ሌሊት ድረስ የማትከፍት ከሆነ “ሙሉ ሥልጣኔዋ ይወድማል” የሚል ዛቻ ካሰሙ ከሰዓታት በኋላ ነው። ለመሆኑ ስምምነቱ ለሁለቱ አገራት ምን ማለት ይሆን?
ቪዲዮ, በየቀኑ አሜሪካንን ሚሊዮኖችን እያስወጣ ያለው ጦርነት
አሜሪካ እና እስራኤል ከኢራን ጋር የጀመሩት ጦርነት ሁለተኛ ወሩን ይዟል። አሜሪካ በጦርነቱ ምን ያህል ገንዘብ እያወጣች ነው? የሚለው ከፍተኛ ትኩረት እየሳበ ይገኛል። የትራምፕ አስተዳደር በቅርቡ ተጨማሪ በጀት እንዲመደብለት ጠይቋል። ይህም ጦርነቱ ምን ያህል ወጪ እያስወጣ ነው? የሚለው ጉዳይ ላይ የበለጠ ግልጽነት እንዲኖር የሚጠይቁ ጥያቄዎች እንዲጨምሩ አድርጓል።
አነጋጋሪ ጉዳይ
የአሜሪካ የኤርትራን ማዕቀቦች ማንሳት፡ ቀይ ባሕር የሸፈነው የሰብአዊ መብት ጥያቄ?
አሜሪካ የኤርትራን ማዕቀቦች ለማንሳት ማቀዷ ሲሰማ ከጀርባ ያለው ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ምክንያት ምንድን ነው? የሚለውን ጥያቄ አጭሯል። ኤርትራ ላይ የሚቀርቡ የሰብአዊ መብት ጥሰት ክሶችን በተመለከተ ተጠያቂነት እና ፍትሕ ሳይሰፍን ማዕቀቦችን ማንሳት ምን ያስከትላል? ለምን አሁን ማዕቀቦችን ማንሳት አስፈለገ? ይህ የአሜሪካ ሐሳብ ለኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ምን ማለት ነው? የሚሉ ጥያቄዎችም እየተነሱ ነው።
የሶማሊያው ፕሬዝዳንት የሥልጣን ዘመናቸው ማብቃቱን ተከትሎ የተፈጠረው አጣብቂኝ
የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ የሥልጣን ዘመናቸውን ለማራዘም ያደረጉትን ሙከራ ተከትሎ ከዚህ ቀደም አጋጥሟቸው አያውቅም የተባለ ከፍተኛ ተቃውሞ እየተጋፈጡ ነው። በአገሪቱ ሕገ መንግሥት መሠረት የፕሬዝዳንቱ የሥልጣን ዘመን የሚያበቃው አርብ ግንቦት 7/2018 ዓ.ም. ነው። ይህ ሁኔታም ሶማሊያን ቀውስ ውስጥ በማስገባት ለአልሻባብ በር ሊከፍት ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
እናት እና ልጅን ጨምሮ ከ30 በላይ ሰዎች የተገደሉበት የመተከል ጥቃት እና ያሳደረው ስጋት
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማክሰኞ ግንቦት 4/2018 ዓ.ም. በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት ከ30 ሰዎች በላይ መገደላቸውን የሟች ቤተሰቦች እና ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ። ይህ በርካታ ሰዎች የተገደሉበት እና ጉዳት የደረሰባቸው ጥቃት የተፈጸመው ከክልሉ ዋና ከተማ አሶሳ መንገደኞችን ባሳፈሩ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ላይ ነው።
አሜሪካ በኤርትራ ላይ ጥላቸው የቆዩ ማዕቀቦች የትኞቹ ናቸው? በተለይ እነማንን ይመለከታሉ?
አሜሪካ በኤርትራ ላይ የጣለቻቸውን ማዕቀቦች ለማንሳት እና ከአሥመራ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማሻሻል ማቀዷ ተዘግቧል። ኤርትራ በኢትዮጵያ ትግራይ ውስጥ በተካሄደው ጦርነት ውስጥ ከነበራት ተሳትፎ ጋር በተያያዘ በአሜሪካ ማዕቀብ ተጥሎባታል። ለመሆኑ አሜሪካ በኤርትራ ላይ የጣለቻቸው ማዕቀቦች የትኞቹ ናቸው?
የትግራይ ሲኖዶስ አክሱምን "ቅድስት ከተማ" ብሎ መሰየሙን እና ይህንኑ የሚያሳዩ "ሕጎችን እያወጣ" መሆኑን አስታወቀ
የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክስርስቲያን ሲኖዶስ ባደረገው ጉባኤ፤ የጥንታዊቷ አክሱም መጠሪያ "ቅድስት አክሱም ጽዮን ከተማ" እንዲሆን መወሰኑን አስታወቀ። ቤተ ክርስቲያኗ፤ ይህንን ውሳኔ ተከትሎ በከተማዋ እንደ "መጠጥ እና ጫት" ሽያጭ ያሉ ተግባራት ላይ ክልከላ እንዲጣል እንደምትፈልግ እንዲሁም "የቅድስና ምልክት እንድታሳይ የሚያደርጉ ሕጎችን" እያወጣች መሆኑን ገልጻለች።
ሌተናንት ጄነራል ታደሰ የትግራይ ክልል የጊዜያዊ አስተዳደር "ሥልጣን በጉልበት እየተያዘ" ነው አሉ
ማክሰኞ ዕለት በተደረገው የትግራይ ክልል የቀድሞ ምክር ቤት ስብሰባ በፕሬዝዳንትነት የተመረጡት ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የሚመራው ካቢኔ ስብሰባ ማድረግ መጀመሩን ተከትሎ፤ ሌተናንት ጄነራል ታደሰ ወረደ የጊዜያዊ አስተዳደሩ "ሥልጣን በጉልበት እየተያዘ" መሆኑን ገለጹ።
የኢትዮጵያ መንግሥት የሱዳን ጦር ያቀረበውን ውንጀላ ውድቅ በማድረግ ሱዳንን "በፀረ ኢትዮጵያ ኃይሎች ማዕከልነት" ወነጀለ
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሱዳን ጦር "ከኢትዮጵያ የተነሱ ድሮኖች ጥቃት ፈጽመዋል" በሚል ያቀረበውን ክስ "መሠረተ ቢስ" እና "በውጭ ኃይሎች ትዕዛዝ የቀረበ" ሲል ውድቅ አደረገ። ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በምላሹ ሱዳን "ለተለያዩ ፀረ ኢትዮጵያ ኃይሎች ማዕከል" መሆኗን እንዲሁም የአገሪቱ ጦር "የህወሓት ቅጥረኛ ተዋጊዎችን እየተጠቀመ" መሆኑን በመግለጽ ከስሷል።
ኢትዮጵያዊ እና ኬንያዊ አትሌቶች ማራቶንን ከሁለት ሰዓት ባነሰ ጊዜ እንዲጨርሱ ያስቻላቸው ምስጢር ምንድን ነው?
ትናንት እሁድ በለንደን የተካሄደው የማራቶን ውድድር ኬንያዊው ሳባስቲያን ሳዌ እና ኢትዮጵያዊው ዮሚፍ ቀጄልቻ ከሁለት ሰዓት በታች ተከታትለው በመግባት ዓለምን አስደምመዋል።
የኢንተርኔት ዳታን በመቆጠብ የቢቢሲ አማርኛ ድረ ገጽን በቀላሉ ማንበብ ይፈልጋሉ?
የቢቢሲ አማርኛን ድረ ገጽ በቀላሉ በመክፈት ዜና እና ታሪኮችን በጽሑፍ ብቻ ያንብቡ!
የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት
በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የአሜሪካንን ባሕር ኃይል እየፈተኑ ያሉት የኢራን ትናንሽ ጀልባዎች
ፕሬዝዳንት ትራምፕ የኢራንን ባሕር ኃይል እንዳወደሙ ቢናገሩም፣ ኢራን ትናንሽ ፈጣን ጀልባዎችን በመጠቀም በሆርሙዝ ወሽመጥ የመርከቦችን እንቅስቃሴን መግታት ችላለች። ስለእነዚህ ውጤታማ የኢራን ፈጣን ወታደራዊ ጀልባዎች ምን እናውያለን?
አሜሪካ እና ኢራን ድል እንደተቀዳጁ እያወጁ ባሉበት ጦርነት አሸናፊው ማን ነው?
አሜሪካ ከኢራን ጋር የምታደርገውን ጦርነት ማቆሟን እየተናገረች ነው። በሁለቱ አገራት መካከል የተኩስ አቁም ከተደረገ ከሳምንታት በኋላ ማክሰኞ ዕለት የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ "ኢፒክ ፊውሪ' በማለት የተጠራው ዘመቻ ማብቃቱን ተናግረዋል።በአሜሪካ እና በኢራን መካከል በተደረገው ጦርነት ማን አሸነፈ?
መሪዎቹ እየተገደሉበት ባለበት ጸንቶ የቀጠለው የኢራን የጦርነት ወቅት አመራር የተዋቀረው እንዴት ነው?
ኢራን በአሜሪካ እና በእስራኤል እየተፈጸመባት ባለው ጥቃት ከጠቅላይ መሪዋ ከአያቶላህ አሊ ኻሜኒ ጀምሮ በርካታ ቁልፍ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ መሪዎቿ ተገድለውባታል። ነገር ግን አመራሯ ሳይፈረካከስ እየተተካካ ፍልሚያውን ቀጥሏል። ለመሆኑ የኢራን አመራር በዚህ ጦርነት ውስጥ ባለበት ጸንቶ እንዴት ሊቀጥል ቻለ?
የሚሳዔል ዒላማ የሆኑት ቅንጡ ከተሞች፡ የኢራን ጦርነት በባሕረ ሰላጤው አገራት ውስጥ ምን ለውጥ ያስከትላል?
የቅንጦት እና የንግድ መናኸሪያዎች ሆነው የቆዩት የባሕረ ሰላጤው አገራት ቅንጡ ከተሞች በኢራን ላይ የተከፈተውን ጦርነት ተከትሎ ገጽታቸው እየተቀየረ ነው። አገራቱ በጦርነቱ ዳር ላይ የቆሙ ቢሆንም በየዕለቱ የኢራን ሚሳዔሎች እየጎበኟቸው ነው። ይህ ጦርነት በወደፊት ገጽታቸው ላይ ምን ውጤት ይኖረዋል?
ኢራን በመካከለኛው ምሥራቅ ፍርሃት የፈጠረችበት ርካሹ ድሮን
አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት መክፈታቸውን ተከትሎ በመካከለኛው ምሥራቅ ውስጥ ጦርነት እየተካሄደ ነው። ኢራን እየተፈጸመባት ላለው ጥቃት አጸፋውን በቀጣናው ባሉ የአሜሪካ ወዳጅ አገራት ላይ እየፈጸመች ነው። ለዚህ ደግሞ ኢራን ርካሽ እና ውጤታማ የሆኑትን ሻሂድ-136 የተባሉ አጥፍቶ ጠፊ ድሮኖችን በስፋት እየተጠቀመች ነው። ይህ በምሥል እና በቪዲዮ የተደገፈው ዘገባ ስለድሮኖቹ ምንነት ይተነትናል።
ከየፈርጁ
'የማያመልጡት ወጥመድ'፡ እናት በመሆናቸው የሚጸጸቱት ሴቶች
. . . "እናትነት ባንፈልገው እንኳ የሚከተለን እና የምናከናውነው ማለቂያ የሌለው ሥራ ነው፣ ምክንያቱም ልጆቻችን በእኛ ላይ ጥገኛ ናቸው… የማናመልጠው ወጥመድ ይመስላል" ትላለች። እናት መሆን ምን ያህል "አስከፊ" እንደሆነም ያለማመንታት ትናገራለች። ስለልጇ ስትጠየቅ ግን ድምጸቷ ጭምር ብሩህ ይሆናል።
ሐረር ውስጥ ለ12 ዓመታት ለመውለድ የሞከረች እናት በአንድ ጊዜ አምስት ሕፃናትን ተገላገለች
ለ12 ዓመታት ልጅ ለመውለድ የሞከረች የሐረሪ ክልል ነዋሪ በአንድ ጊዜ አምስት ልጆችን መገላገሏ ተገለጸ። በድሪያ አደም የተባለችው እናት እሷና ባለቤቷ "በአንድ ጊዜ አምስት ልጆች ስላገኙ እጅግ እንደተደሰቱ" ተናግራለች።
ያለባቸው የጤና ችግር ሕክምና እንዲያጠኑ ያደረጋቸው ኢትዮጵያውያን ወጣቶች
በረከት በቀለ፣ ኪምቢፊዳ በሚል ስም ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ይታወቃል። ወደ ቲክቶክ ብቅ ከማለቱ አስቀድሞ "በስፓይና ቢፊዳ (spina befida) የተያዝኩ ብቸኛው ሰው እኔ ብቻ እንደሆንኩ ይሰማኝ ነበር" ይላል። የአሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት መሥራቹ ዶ/ር ነቢያት ተስፋዬም ልክ እንደ በረከት ሁሉ ከስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) ጋር ነው የተወለደው። አሁን 33 ዓመት እንደሆነው የሚናገረው ዶ/ር ነቢያት፣ በተወለደ በ22ኛው ቀን የስፓይና ቢፊዳ የቀዶ ሕክምና ተደርጎለታል። ሁለቱም ወጣቶች ከራሳቸው ህመም ተነስተው ሕክምና ለማጥናት መወሰናቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ቢቢሲ አማርኛን በዋትስአፕ ላይ ያግኙ
አጃኢብ!
አባቱን ገድሎ 12 ዓመት የተፈረደበት ልጅ ይቅርታ እንዲደረግለት የሚጠይቀው ቤተሰብ
የ27 ዓመቷ ሳራ ከእንባዋን ጋር እየታገለች ለግድያው ምክንያት የሆነውን አሳዛኝ ክስተት ለቢቢሲ ተናግራለች። ካርሎስ ለዓመታት ሞይሰስን እንደደበደበና አካላዊ ጥቃት እንደፈጸመበት የሰማችው ያኔ ነበር።
በአፍሪካ የፊልም አዋርድ ላይ የታየው ከ500 ዳቦዎች የተሰራው ቀሚስ
እሁድ ግንቦት 2 2018 ዓ.ም. በናይጄሪያ በተካሄደው 12ኛው የአፍሪካ ፊልሞች አዋርድ ላይ ታዋቂ ሰዎች፣ የፊልም ባለሙያዎች እንዲሁም የማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች በተለያዩ አልባሳት ተውበው ተገኝተዋል። በዕለቱ ከተገኙት ስመ ጥር ሰዎች ሁሉ ግን የአንዷ ታዋቂ የቴሌቪዥን ተዋናይ አልባሳት የበለጠ መነጋገሪያ ሆኖ አምሽቷል።
የተመለሱ ጥያቄዎች
አስፈላጊ ነገር ግን ጎጂ የሆነውን የጨው አወሳሰዳችንን እንዴት መመጠን እንችላለን?
ጨው ምግባችንን የበለጠ ያጣፍጠዋል። ለሰው ልጅ ሕይወትም አስፈላጊ ነው። በጨው ውስጥ የሚገኘው ሶዲየም በሰውነት ውስጥ የሚኖረውን ትክክለኛውን የውሃ መጠን ለመጠበቅ በጣም አስፈላጊ ነው። ህዋሳትም ንጥረ ምግቦችን እንዲወስዱ ይረዳል። በምግብ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩረው የቢቢሲ ወርልድ ሰርቪስ ፕሮግራም “ዘ ፉድ ቼይን” ጨው በሰውነታችን ውስጥ ያለውን ወሳኝ ሚና እና ለአንድ ሰው ከመጠን በላይ የሚባለው የጨው ፍጆታ ምን ያህል ነው የሚለውን ተመልክቷል።
ከሆርሙዝ በፊት ዓለም ላይ ምን ያህል የባሕር እንቅስቃሴ እገዳዎች ተጥለዋል? ምን ያህል ውጤታማ ነበሩ?
አሜሪካ ወደ ኢራን ወደቦች የሚገቡ እና የሚወጡ መርከቦች ላይ እገዳ መጣሏ ጥንታዊ የወታደራዊ ጫና መፍጠሪያ ስልትን መልሶ ያመጣ ነው። ይህ እርምጃ የባሕር መስመሮችን በመዝጋት ምጣኔ ኃብታዊ ጫና መፍጠር፣ ንግድን ማስተጓጎል እና ተገዳዳሪው አካል አቋሙን እንዲቀይር ወይም እጅ እንዲሰጥ የማስገደጃ ስልት ነው። ታሪክ የሚያሳየን እንዲህ ዓይነት ስልቶች ጫና በመፍጠር ረገድ ውጤታማ ቢሆኑም ሰፊ ተጽዕኗቸው ግን ከሚታሰበው በላይ ውስብስብ መሆኑን ነው።














































































































